Skip to main content

ያለፉት ሶስት ዓመታት ጉዞ ድልም ፈተናም ነበረው:- ርዕሰ መስተዳድር 

እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) 

ሆሳዕና፣ሐምሌ 30/2018፦ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች 

ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 6ኛ መደበኛ ጉባኤ በወልቂጤ 

ከተማ እየተካሔደ ነው 

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) 

እንደገለጹት እያንዳንዱ ስራ ላይ ከ10 እስከ 15 በመቶ በመጨመር እቅድ 

ተዘጋጅቷል ብለዋል። 

የክልሉን የመልማት አቅም በጥናት መለየት ተችሏል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ 

ይህም የምርታማነት መጠን ለማሳደግ እንደሚረዳ አስረድተዋል። 

የበጀት ዓመቱን የዝግጅት ምዕራፍ አስቀድሞ ተግባራዊ ማድረግ ስለመቻሉም 

ርዕሰ መስተዳድሩ በንግግራቸው ጠቅሰዋል። 

አዳዲስ ሀሳቦችን በማፍለቅ ለተሻለ ለውጥ የሚተጋ አመራር እና ፈጻሚ መፍጠር 

ስለመቻሉም ጠቅሰዋል። 

ያለፉት ሶስት ዓመታት ጉዞ ፈተናም ድልም ነበረው:- ፈተናዎችን ወደ ድል የመቀየር 

ስትራቴጂ ተቀርጿል ብለዋል። 

በክልሉ መሰረታዊ የሆኑ ችግሮችን መፍታት ተችሏል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ ስራን 

መሰረት ያደረገ የአመራር ስርዓት ተፈጥሯል። 

የክልሉ መንግስት የህዝብ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች 

ላይ ትኩረት ማድረጉን ጠቅሰዋል። 

የትምህርት ስራ በጊዜ ሂደት እየተሻሻለ እንደሚሄድ ርዕሰ መስተዳድሩ በማብራሪያቸው 

ገልጸዋል። 

በመምህራን፣በትምህርት አመራር፣በግብአት አቅርቦት እንዲሁም በስርዓተ ትምህርት 

ላይ በትኩረት መስራት ተገቢ ስለመሆኑም ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል። 

ባለፉት ሁለት ዓመታት ከተረጂነት ወደ ምርታማነት መሸጋገር የሚያስችል አቅም መፍጠር 

ተችሏል ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል። 

ከመኖሪያ ቤት ቦታ አቅርቦት ጋር በተያያዘ በሆሳዕና ከተማ ለ285 ማህበራት በተቀመጠው 

ቅደም ተከተል መሰረት ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ስለመሆኑም ጠቅሰዋል። 

በክልሉ በተለያዩ ከተሞች ከ200 ኪ/ሜ በላይ የኮሪደር ልማት ስራ ተግባራዊ እየተደረገ 

ስለመሆኑም ጠቅሰዋል። 

የጠራ አስተሳሰብ እና ተግባር ባለባቸው ዘርፎች ውጤት ተመዝግቧል ያሉት ርዕሰ 

መስተዳድሩ በተቃራኒው ደግሞ ዝቅተኛ አፈጻጸም ተመዝግቧል። 

በብልጽግና እሳቤ ውስጥ ሆኖ ተግባርን መምራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ የጋራ ተግባቦት 

ስለመፈጠሩም ጠቅሰዋል። 

ሰባተኛው ሀገር አቀፍ ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማ በሆነ መንገድ መጠናቀቁን አብራርተዋል። 

የምክር ቤት አባላት በጋራ ትርክት ግንባታ ላይ ሚናቸውን እንዲወጡም ርዕሰ መስተዳድሩ 

ጥሪ አቅርበዋል። 

የጋራ ትርክት ለሀገረ መንግስት እና ለተቋም ግንባታ የሚኖረው አበርክቶ የላቀ ስለመሆኑም 

ርዕሰ መስተዳድሩ አመላክተዋል። 

የኑሮ ማረጋጋት እና የስራ እድል ፈጠራ ላይ በትኩረት መስራት ይገባል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ 

ከሰንበት እስከ ሰንበት እና የምርት አቅርቦት ማሳደግ ወሳኝ መሆኑን አመላክተዋል። 

የከተሞችን እድገት ለማፋጠን የገቢ መሰረትን ማስፋት እና ኢከኮሚው የሚያመነጨውን ገቢ 

መሰብሰብ ተገቢ ስለመሆኑም ርዕሰ መስተዳድሩ አስረድተዋል። 

የክልሉን ከተሞች ተወዳዳሪ እና የኮንፈረንስ ማዕከል ለማድረግ የጋራ ጥረት እንደሚጠይቅም 

ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቅሰዋል።

Image