Skip to main content

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት 3ተኛ ዙር 

የፅዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው

ሆሳዕና ፣ነሐሴ 11/2018 ፦ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ 

መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ( ዶ/ር ) በተገኙበት 3ተኛ ዙር 

"ፅዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ" በሚል መርህ የንቅናቄ መድረክ 

በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው

ጽዱ ኢትዮጵያን ለትውልድ ማስተላለፍን መሰረት ባደረገው 

ፕሮግራም ለአካባቢ መቆሸሽ እና ብክለት መንስኤ የሆኑ ችግሮችን 

በጋራ መከላከል ላይ ማተኮር ተገቢ መሆኑ ተመላክቷል።

በመድረኩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 

ዋና አፈ-ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ፋጤ ሱርሞሎ፣የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት 

ፕሬዘዳንት ኤርሲኖ አቡሬ፤የኢፌዲሪ ደን አከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ምክትል 

ዋና ዳይሬክተር ፍሬነሽ መኩሪያ ጨምር የክልሉ ከፍተኛ የቢሮ ኃላፊዎችና 

ጥሪ የተደረገላች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

Image