Skip to main content

 

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር 

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መርቀው ለሥራ ክፍት አደረጉ

ሆሳዕና ፣ ሰኔ 9 / 2018 ፦የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል 

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በሆሳዕና ከተማ 

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መርቀው ሥራ አስጀምረዋል፡፡

የሆሳዕና የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በውስጡ 

6 ተቋማት የያዘ ሲሆን በአጠቃላይ 20 የተለያዩ አገልግሎቶችን ይሰጣል።

በምረቃ መርሐ ግብሩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ 

ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ፣

የክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ኤርሲኖ አቡሬ .

ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ፣

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክላስተር አስተባባሪዎች፣

የሀድያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቲዎስ አኒዮ፣

ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

 

Image