Skip to main content
“በጎነት ከውስጥ መልካምነት የሚመነጭና ሀገርን ወደ ላቀ ከፍታ የሚያሻግርታላቅ አገልግሎት ነው”፦ ርዕሠ መስተዳድር እንዳሻውጣሰው(ዶ/ር)

“በጎነት ከውስጥ መልካምነት የሚመነጭና ሀገርን ወደ ላቀ ከፍታ 

የሚያሻግርታላቅ አገልግሎት ነው”፦ ርዕሠ መስተዳድር 

እንዳሻውጣሰው(ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ሐምሌ 3/2018 ፦"በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ሀሳብ 

የሚንቀሳቀሰውሀገር አቀፍ የወሰን ተሻጋሪ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት 

ቡድንበሆሳዕና ከተማ ሲደርስ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል።

በዕለቱ በተዘጋጀው የአቀባበል መረሐ ግብር ላይ የተገኙት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ 

ክልልርዕሠ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ለበጎ ፈቃደኞቹ የእንኳን 

ደህናመጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

“በጎነት ከውስጥ መልካምነት የሚመነጭና ሀገርን ወደ ላቀ ከፍታ የሚያሻግር 

ታላቅአገልግሎት ነው ሲሉ ርዕሠ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) ተናግረዋል።

በጎፈቃደኝነት በኢትዮጵያ ውስጥ እንደ 'ፒስ ኮር' (Peace Corps) እና የ'ስካውት' 

ንቅናቄዎችያሉየረጅም ጊዜ ታሪካዊ መሠረቶች ያሉት መሆኑን አስታውሰዋል። 

ይህ መልካምእሴት በአሁኑ ወቅት ከለውጡ በኋላ በተከታታይና በተጠናከረ 

መልኩእየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ይህመርሃ ግብር የወደፊቷን ኢትዮጵያ የሚረከቡ ወጣቶች ማህበረሰባቸውንና 

ሀገራቸውንበቅርበት እንዲረዱ፣ እርስ በእርስ የዕውቀትና የባህል ልውውጥ 

እንዲያደርጉምቹዕድል የሚፈጥር መሆኑን አስገንዝበዋል።

በሌሎች ሀገራት ሰዎች እስከ 70 እና 80 ዓመታቸው ድረስ በጉልበት ሀገራቸውን 

እንደሚያገለግሉበመጥቀስ፣ የሀገራችንም ወጣቶች የአገልግሎት ዘመናቸውን 

ማራዘምእንዲችሉ ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ ጥሪ አቅርበዋል።

አያይዘውም ከሀምሌ 28 ቀን ጀምሮ የሚካሄደውን ታሪካዊ ሀገራዊ ምክክር 

ወጣቶችበሀሳብና በሁሉም ረገድ እንዲደግፉ በጥብቅ አሳስበዋል።

ኢትዮጵያውያን መክረውና ተስማምተው እንዲወጡ የበጎ ፈቃድ ቡድኑ አባላት 

የበኩላቸውንአዎንታዊ ሚና እንዲጫወቱ ጥሪ አቅርበዋል።

ርዕሠ መስተዳድሩ በንግግራቸው ማጠቃለያ ላይ በጎ ፈቃደኞቹ  የመጡበትን 

መልካምየልማትና የአገልግሎት ዓላማ በተሳካ ሁኔታ እንዲወጡና ቆይታቸው 

የሰላምና ፍሬያማ እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።

Read more
የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አተገባበር በጠንካራ የአመራር ስርዓትና በቅርብ ክትትል ተመርቷል፤ የተሻሉ ውጤቶችም ተመዝግበዋል:- ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር

የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አተገባበር በጠንካራ የአመራር ስርዓትና 

በቅርብ ክትትል ተመርቷል፤ የተሻሉ ውጤቶችም ተመዝግበዋል:- 

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር)

ሆሳዕና ፣ ሐምሌ 3/2018፦ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር 

እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የዞኖች እና የልዩ ወረዳዎችን የ2018 በጀት ዓመት 

ዕቅድ አፈጻጸም በጽሕፈት ቤታቸው ዛሬ ገምግመዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በመድረኩ እንደገለጹት፣የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ 

አተገባበር በጠንካራ የአመራር ስርዓትና በቅርብ ክትትል ተመርቷል፤ 

የተሻሉ ውጤቶችም ተመዝግበዋል። 


የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ከቅድመ ዝግጅት ጀምሮ በሁሉም መዋቅሮች 

በተቀናጀ መንገድ መመራቱም በጥንካሬ የሚጠቀስ መሆኑንም 

ርዕሰ መስተዳድሩ አመልክተዋል።

ለተግባራቱ የተደረገው የድጋፍና የክትትል ሥራም የተጠናከረ መሆኑን ጠቅሰው፣ 

በሂደቱም በርካታ ውጤቶች ተመዝግበዋል ብለዋለል።

በሁሉም አካባቢዎች ሥራዎች በቅርብ ክትትል መመራታቸውን ያስታወቁት 

ርዕሰ መስተዳድሩ፣ የግልና የጋራ ጥረቶችን በማቀናጀት እና የታዩ ክፍተቶችን 

በፍጥነት በማረም ውጤታማ ሥራ መሠራቱን ገልጸዋል።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በምርታማነትና በገቢ ማሳደግ ረገድ ጉልህ ውጤቶች 

መመዝገባቸውን ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው(ዶ/ር) ጠቁመው፣ የህብረተሰቡ 

ተሳትፎና ተጠቃሚነት እያደገ መምጣቱን አስረድተዋል።

የመልካም አስተዳደር ጉዳዮችን አጀንዳ ማድረግ፣ የኑሮ ውድነትን ማረጋጋት፣ 

የገቢ አቅምን በሙሉ መጠቀም፣ ኢኒሼቲቮችን ማጠናከር፣ ምርታማነትንና 

የመረጃ ጥራትን ማሻሻል በቀጣይ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች መሆናቸውን 

ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።

በተጨማሪም የህዝብ ተሳትፎን ማሳደግ፣ አመራሩና ሰራተኞች ሙሉ 

ሰዓታቸውን ለሥራ እንዲያውሉ ማድረግ እንዲሁም የህዝቦችን አንድነት 

ለማጠናከር ተከታታይነት ያላቸው ሥራዎችን ማከናወን ቀጣይ ትኩረት 

የሚሹ ጉዳዮች ስለመሆናቸውም አስገንዝበዋል።

Read more
ክቡር ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በተገኙበት የዞንና ልዩ ወረዳ መዋቅሮችን የ2018 በጀት አመት የተጠቃለለ ዕቅድ አፈፃፀም እየገመገሙ ነው

ክቡር ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በተገኙበት 

የዞንና ልዩ ወረዳ መዋቅሮችን የ2018 በጀት አመት የተጠቃለለ 

ዕቅድ አፈፃፀም እየገመገሙ ነው።

ሆሳዕና ፣ ሐምሌ 3 /2018 ፦ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ 

መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ( ዶ/ር ) የክልሉን ዞኖችና ልዩ ወረዳ 

መዋቅሮች የ2018 በጀት አመት የተጠቃለለ ዕቅድ አፈፃፀም 

በጽህፈት ቤታቸው እየገመገሙ ይገኛሉ።

በክልሉ የሚገኙ የዞንና የልዩ ወረዳ አስተዳዳሪዎች የ2018 በጀት አመት 

የተጠቃለለ ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርታቸውን እያቀረቡ ይገኛል።

የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርቱ በዝርዝር ቀርቦ ውይይት ከተደረገበት በኋላ 

ለ2019 በጀት አመት አቅጣጫ ይቀመጣል ተብሎም ይጠበቃል።

Read more
በክልሉ የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል በተሰራው ስራ ካለፉት ዓመታት የተሻለ ለውጥ ይጠበቃል - ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

በክልሉ የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል በተሰራው ስራ 

ካለፉት ዓመታት የተሻለ ለውጥ ይጠበቃል - ርዕሰ 

መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፣ ሐምሌ 1/2018 ፦የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር

እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) 3ኛውን ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ የ12ኛ ክፍል ሀገር 

አቀፍ ፈተና በዋቸሞ ዩኒቨርስቲ አስጀምረዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት የፈተና አሰጣጥ በሀገር አቀፍ ደረጃ 

ከዚህ ቀደም ከምናውቀው የምዘና ዘዴዎች ወደ ዲጅታል በመለወጥ ላይ 

ይገኛል።

በክልላችንም በ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከሚወስዱ 

ከአጠቃላይ ተፈታኞች ውስጥ 61 በመቶው በበይነ-መረብ እንደሚወስዱ ገልጸዋል።

ይሄም በክልል ባለፉት ዓመታት ከነበረው በበይነ መረብ ፈተና የመስጠት አቅም

በእጅጉ ያደገ ነው ብለዋል።

በሚቀጥለው ዓመት ዩኒቨርሲቲዎች፣ ኮሌጆችን ጨምሮ በትምህርት ቤቶች 

በቂ ዝጅግት ተደርጎ ቁጥሩ ለማሳደግ ይሰራል ነው ያሉት።

በክልሉ ተማሪዎችን ለፈተና ለማዘጋጀት ልዩ ልዩ ስራዎች መሰራታቸውን የገለጹት 

ርዕሰ መስተዳድሩ የተማሪዎች የክፍል ውስጥ ምዘና ውጤት ከመከታተል ጀምሮ 

የውጤት ማሻሻያ ስልቶችን በመቅረጽ ተግባራዊ ስለመደረጉ ገልጸዋል።

በተለይም በክልሉ በተከታታይ ዓመት አንድም ተማሪ ማሳለፍ ካልቻሉ ትምህርት 

ቤቶች የማለፍ ተስፋ ያላቸው 886 ተማሪዎች በዩኒቨርስቲ ገብተው ልዩ የማጠናከሪያ 

ትምህርት እንደተሰጣቸው ተናግረዋል።

የእነዚህ ስራዎች ድምር ውጤት በተማሪዎች ውጤትና ስነ ምግባር ላይ ለውጥ 

ያመጣል ተብሎ እንደሚጠበቅ ያላቸውን ዕምነት ገልጸዋል።

Read more
ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በዋቸሞ ዩኒቨርስቲ ተገኝተው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን አስጀምረዋል። ሆሳዕና ፣ ሐምሌ 1/2018፦የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በዋቸሞ ዩኒቨርስቲ ተገኝተው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የዚህን ዙር ተፈታኞችን ፈተና በማስጀመር አበረታተዋል። ሀገር አቀፍ ፈተናው ከሰኔ 23 ቀን 2018 ዓመተ ምህረት

ርዕሰመስተዳድርእንዳሻውጣሰው (ዶ/ር) በዋቸሞዩኒቨርስቲተገኝተው

የ12ኛክፍልሀገርአቀፍፈተናንአስጀምረዋል።

ሆሳዕና፣ሐምሌ 1/2018፦የማዕከላዊኢትዮጵያክልልርዕሰመስተዳድር

እንዳሻውጣሰው (ዶ/ር) በዋቸሞዩኒቨርስቲተገኝተው የ12ኛክፍልሀገር

አቀፍፈተናየዚህንዙርተፈታኞችንፈተናበማስጀመርአበረታተዋል።


ሀገርአቀፍፈተናውከሰኔ 23 ቀን 2018 ዓመተምህረትጀምሮበተለያዩዙሮች

እየተሰጠመሆኑየሚታወስሲሆን፤ለተፈጥሮሳይንስተማሪዎችበሶስትዙሮች

እናለማህበራዊሳይንስተማሪዎችምበተተመሳሳይበሶስትዙሮችእየተሰጠ

መሆኑተገልጿል።

የ12ኛክፍልሀገርአቀፍፈተናአጀማመሩላይምክትልርዕሰመስተዳድርእና

የማህበራዊክላስተርአስተባባሪአቶአንተነህፍቃዱእናየዋቸሞዩኒቨርስቲ

የማኔጅመንትአባላትተገኝተዋል።

ሆሳዕና፣ሐምሌ 1/2018፦የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር

እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በዋቸሞ ዩኒቨርስቲ ተገኝተው የ12ኛ ክፍል ሀገር

-አቀፍ ፈተና የዚህን ዙር ተፈታኞችን ፈተና በማስጀመር አበረታተዋል።


ሀገር-አቀፍ ፈተናው ከሰኔ 23 ቀን 2018 ዓመተ-ምህረት ጀምሮ በተለያዩ ዙሮች

እየተሰጠ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን፤ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በሶስት ዙሮች

እና ለማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎችም በተተመሳሳይ በሶስት ዙሮች እየተሰጠ

መሆኑ ተገልጿል።

የ12ኛ ክፍል ሀገር-አቀፍ ፈተና አጀማመሩ ላይ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና

የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ አቶ አንተነህ ፍቃዱ እና የዋቸሞ ዩኒቨርስቲ

የማኔጅመንት አባላት ተገኝተዋል።

Read more
ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)በቡታጅራ ከተማ ከሰንበት እስከ ሰንበት የገበያ ማዕከል መርቀው ስራ አስጀመሩ

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)በቡታጅራ ከተማ 

ከሰንበት እስከ ሰንበት የገበያ ማዕከል መርቀው ስራ አስጀመሩ 

ሆሳዕና፣ሰኔ 30/2018 ፦የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር 

እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በምስራቅ ጉራጌ ዞን በቡታጅራ ከተማ ከሰንበት 

እስከ ሰንበት የገበያ ማዕከል መርቀው ስራ አስጀምረዋል 

በቡታጅራ ከተማ የተገነባው ከሰንበት እስከ ሰንበት የግብይት ማዕከል 

15 ሚሊየን ብር ወጪ ተደርጎበታል። 

የግብይት ማዕከሉ ሳምንቱን ሙሉ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ሲሆን 

አምራቹን እና ሸማቹን ማህበረሰብ በቀጥታ በማገናኘት የኑሮ ውድነቱን 

በማረጋጋት ረገድ የጎላ ሚና እንዳለውም ተጠቁሟል። 

በማዕከሉ የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርት ቀርቦ ግብይት 

እየተካሔደበት ነው።

 

Read more
ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በቡታጅራ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መርቀው ስራ አስጀመሩ

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በቡታጅራ ከተማ 

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መርቀው ስራ አስጀመሩ 

ሆሳዕና ፣ ሰኔ 30/2018፦ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር 

እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በቡታጅራ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል 

አገልግሎት መርቀው ስራ አስጀመሩ 

በማዕከሉ በመጀመሪያ ዙር በ6 ተቋማት 22 አገልግሎት እየተሰጠ 

መሆኑም ተመላክቷል። 

በርዕሰ መስተዳድሩ የተመራው ልኡክ በማዕከሉ እየተሰጠ ያለውን 

አገልግሎት ተመልክተዋል።

Read more
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የዘንድሮው ክልል አቀፍ የተቀናጀ የመኸር ግብርና ልማት ንቅናቄ ከቀናት በፊት በይፋ ተጀምሯል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የዘንድሮው ክልል አቀፍ የተቀናጀ 

የመኸር ግብርና ልማት ንቅናቄ ከቀናት በፊት በይፋ ተጀምሯል። 

ከዝናቡ ሁኔታ ጋርም የተያያዙ ስጋቶች በተወሰነ ደረጃ እየተፈቱ ይመስላል፤

ሁሉንም ዕድሎች፣አቅሞችና ፀጋዎች አጣጥሞ፣መኸሩን ለተሻለ ምርታማነት 

መጠቀም ይጠበቃል።

Read more
ሁለንተናዊ የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ጥረቶች ያለአንዳች መዘናጋት ተጠናክረው ይቀጥላሉ ፦ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )

ሁለንተናዊ የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ጥረቶች 

ያለአንዳች መዘናጋት ተጠናክረው ይቀጥላሉ ፦

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )

ሆሳዕና ፣ሰኔ 22 ፣2018፦የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር 

እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)፣ በልዩ ትኩረት እየተመሩ የሚገኙ ተግባራትን 

ወቅታዊ የአፈጻጸም ደረጃ በበይነ መረብ አማካይነት ዛሬ ገምግመዋል፤ 

ቀጣይ አቅጣጫዎችም ተመላክተዋል።

የአፈጻጸም ግምገማው በፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ፣ በመሶብ - የአንድ 

ማዕከል አገልግሎት ማዕከላት ዝግጅት ፣በኢትዮ - ኮደርስ ስልጠና፣ 

በገቢ አሰባሰብ ፣በከተማና በገጠር ኮሪደር ልማት ፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ 

ስራዎች አፈጻጸም፣ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት እና ኑሮ ውድነትትን 

ማረጋጋት በተመለከቱ ጉዳዮች ዙሪያ መሆኑ ተመልክቷል።

የተግባራቱን ወቅታዊ አፈጻጸም ደረጃ የተመለከተ ሪፖርት በሚመለከታቸው 

ቢሮዎች ኃላፊዎች በኩል ቀርቦ ውይይት ተደርጓል።

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)፣ በመድረኩ ማጠቃለያ እንደገለፁት ፤ 

ሁለንተናዊ የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ጥረቶች ያለአንዳች 

መዘናጋት ተጠናክረው ይቀጥላሉ።


እየተጠናቀቀ በሚገኘው በጀት ዓመት ቀሪ ጊዜያትም ይሁን በመጪው አዲሱ በጀት ዓመት ፣ 

በሁሉም መስኮች የህዝቦችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማሳደግ የየደረጃው አመራር በትጋት 

መንቀሳቀስ የሚጠበቅበት መሆኑን ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) 

አፅንኦት ሰጥተው አሳስበዋል ።

በሁለተኛው ዙር መሶብ - የአንድ ማዕከል አገልግሎት እንቅስቃሴ የወራቤ፣ የወልቂጤ፣ 

የሆሳዕና ፣ የሀላባ ቁሊቶ እና የዱራሜ ከተሞች ማዕከላት ተጠናቅቀው ለአገልግሎት 

ክፍት መሆናቸው በመደረኩ የተጠቀሰ ሲሆን ፣የቡታጅራ ከተማ ማዕከልም ከጥቂት 

ቀናት በኋላ ተጠናቅቆ ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆን ተገልጿል። 


ተጠናቅቀው ለአገልግሎት ክፍት የሆኑ ማዕከላት ወደተሟላ መንግስታዊ አገልግሎት 

መስጠት ስለመግባታቸዉ በየመቅሩ የቅርብ ክትትል እንዲደረግ አቅጣጫ ተቀምጧል ።
ከፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ አንፃር እስከ ሰኔ 20 ቀን 2018 ዓመተ ምህረት ድረስ ባለው 

ጊዜ በክልሉ ከ3 ሚሊየን 1መቶ ሺህ በላይ ያህል ዜጎች የፋይዳ መታወቂያ መውሰዳቸው 

በመድረኩ ተገልጿል ።

የኢትዮ - ኮደርስ ስልጠናውም ተጠናክሮ መቀጠሉ በውይይቱ የተዳሰሰ ሲሆን፣ 

ሰልጣኞች ስልጠናውን በአግባቡ አጠናቅቀው ሰርተፍኬት የሚወስዱበት ሁኔታ በትኩረት 

እንዲመራ አቅጣጫ ተቀምጧል።

ከገቢ አሰባሰብ አንፃር እስከ ሰኔ 20 ቀን 2018 ዓመተ ምህረት ድረስ 24 ነጥብ 7 

ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡ የተጠቀሰ ሲሆን፣ይህም በበጀት ዓመቱ ለመሰብሰብ 

ከታቀደው 27 ቢሊየን ብር ዕቅድ አንፃር አፈጻጸሙ 91 ነጥብ 5 በመቶ መደረሱን 

ያመለክታል ተብሏል ።

በከተማ እና በገጠር ኮሪደር ልማት ፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ ስራዎች አፈጻጸም፣ የክረምት 

በጎ ፈቃድ አገልግሎት እና ኑሮ ውድነትትን ማረጋጋትን በተመለከቱ ጉዳዮች ወቅታዊ 

አፈፃፀም ሁኔታ ዙሪያ ዝርዝር ውይይት ተደርጓል ፤ ቀጣይ አቅጣጫዎችም ተቀምጠዋል።

በመድረኩ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ዶክተር 

ዲላሞ ኦቶሬን ጨምሮ የክልሉ አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት፣ የክልሉ ካብኔ አባላት፣ 

የዞኖች እና ልዩ ወረዳዎች ዋና አስተዳዳሪዎች እና አስተባባሪ ኮሚቴዎች እንዲሁም 

ሌሎችም ከፍተኛ አመራሮች ተሳትፈዋል።

Read more
ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ዶ/ር በዱራሜ ከተማ መሶብ - የአንድ ማዕከል አገልግሎት መርቀው ከፈቱ።

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ዶ/ር በዱራሜ ከተማ 

መሶብ - የአንድ ማዕከል አገልግሎት መርቀው ከፈቱ።

ሆሳዕና ሰኔ 19 ፣ 2018 ዓ.ም የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል 

መንግስት ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ( ዶ/ ር ) 

በከንባታ ዞን ዱራሜ ከተማ የተገነባውን መሶብ - የአንድ ማዕከል 

በዛሬው እለት መርቀው ከፈቱ።

"መሶብ-የአንድ ማዕከል አገልግሎት " በአንድ ጣራ ስር የተለያዩ 

የመንግስት አገልግሎቶችን በማጣመር የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን 

በመጠቀም አገልግሎት እንደሚሰጥ ተመላክቷል።

የአሰራር ስርዓቱ ዜጎች የተሟላ የዲጂታል አማራጮችን በመጠቀም 

በቀላሉ የተለያዩ የመንግስት ተቋማትን አገልግሎት እንዲያገኙ እንደሚያስችል 

ተመላክቷል።

መሶብ - የአንድ ማዕከል አገልግሎት በአንድ ስፍራ በ6 ተቋማት 

20 አገልግሎቶችን እንደሚሰጥ ተመልክቷል።

 

 

Read more