Skip to main content
የተከበራችሁመላውየማዕከላዊኢትዮጵያክልልሕዝቦች፣ የየደረጃውአመራሮች፣የብልፅግናፓርቲአባላትእናደጋፊዎች፣ ተፎካካሪፓርቲዎች፣የፀጥታአካላት፣በአጠቃላይመላውየሕብረተሰብክፍሎች፣

የተከበራችሁ መላው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝቦች፣

የየደረጃው አመራሮች ፣ የብልፅግና ፓርቲ አባላት እና ደጋፊዎች፣

ተፎካካሪ ፓርቲዎች ፣ የፀጥታ አካላት ፣ በአጠቃላይ መላው የሕብረተሰብ ክፍሎች፣

ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ፣ በእናንት ኃላፊነት በተሞላበት ንቁ የዜግነት ተሳትፎ፣

ሀገርን የማስቀደምና የማስቀጠል ፅናትና የአስተዋይነት መንፈስ ታጅቦ

በሠላማዊና በሠከነ ሁኔታ ተጠናቅቋል ፤ኢትዮጵያ መርጣለች!


የሀገራችን_ ኢትዮጵያ፣ተስፋዋ እንዲለመልም፣፣ልዕልናዋ እንዲፀና፣መፃኢ ዕጣፈንታዋ

ብሩህ እንዲሆን አኩሪ አስተዋጽኦ አበርክታችኋል፤


ብርድ ፣ፀሐይና ዝናቡንም ተቋቁማችሁ፣ታሪክ ሠርታችኋል ፣ ለዴሞክራሲ

ግንባታው ሂደት ማበብ ጉልህ ዐሻራ አኑራችሁዋል፤


ለዚህከፍተኛ አስተዋጽኦ፣በክልሉ መንግስት እና በእራሴስም፣

ምስጋናዬን በታላቅ አክብሮት አቀርባለሁ።

በሕዝቦች ንቁ ተሳትፎና ዐሻራ የጀመርነዉ የዴሞክራሲ፣የሠላም እና የልማት ግንባታ

ወደ አዲስ ምዕራፍ ይሸጋገር ዘንድ መላው ሕዝባችን የጀመረዉ ንጥረት አጠናክሮ

እንዲቀጥል ጥሪ አቀርባለሁ!

 
አመሠግናለሁ!

 

Read more
ርዕሰመስተዳድርእንዳሻውጣሰው (ዶ/ር)በወራቤከተማ ከሰንበትእስከሰንበትየገበያማዕከልመርቀውስራአስጀመሩ

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በወራቤ ከተማ

ከሰንበት እስከ ሰንበት የገበያ ማዕከል መርቀው ስራ አስጀመሩ

Read more
በሌማት ትሩፈት ከቤተሰብ እና ከማህበረሰብ ተጠቃሚነት ባለፈ ወደ ፋብሪካ መሸጋገር እንደሚቻል ተመልክተናል :- ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

በሌማት ትሩፈት ከቤተሰብ እና ከማህበረሰብ ተጠቃሚነት ባለፈ 

ወደ ፋብሪካ መሸጋገር እንደሚቻል ተመልክተናል :-

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) 

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018፦የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር

 እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በሀዲያ ዞን የሊቻ ሁለገብ የገበሬዎች ህብረት ስራ

 ዩኒየን የወተት ማምረቻ፣ማቀነባበሪያ እና የግብይት ማዕከል ስራ አስጀመሩ 

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት በክልሉ የወተት ማቀነባበሪያዎች ስራ መጀመር

የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ያሳድጋል ብለዋል። 

የሊቻ ሁለገብ የገበሬዎች ህብረት ስራ ዩኒየን ከዚህ ቀደም በዘርፉ 

የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከተ ስለመሆኑም ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል። 

አሁን በትንሽ አቅም የተጀመረው ጥረት የወተት እና የወተት ተዋጽኦዎች 

በማምረት በኢኮኖሚው ላይ የሚኖረው አበርክቶ ከፍተኛ መሆኑን አብራርተዋል። 

ማቀነባበሪያው አርሶ አደሩን የፋብሪካ ባለቤት በማድረግ ኢኮኖሚያዊ 

ተጠቃሚነቱን እንደሚያሳድግሞም ጠቁመዋል። 

የወተት እና የወተት ተዋጽኦው በክልሉ በሁሉም አካባቢዎች ተደራሽ 

እንዲሆን በልዩ ትኩረት መስራት እንደሚገባም ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል። 

የሌማት ትሩፈት ከቤተሰብ እና ከማህበረሰብ ተጠቃሚነት ባለፈ ወደ 

ፋብሪካ መሸጋገር እንደሚቻል ተመልክተናል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ 

ምርቶቹን ወደ ሌሎቹ የሀገሪቱ ክልሎች ማስፋፋት ይገባል ብለዋል።

Read more
ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)በሀዲያ ዞን የሊቻ ሁለገብ የገበሬዎች ህብረት ስራ ዩኒየን የወተት ማምረቻ፣ማቀነባበሪያ እና የግብይት ማዕከል ስራ አስጀመሩ

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)በሀዲያ ዞን የሊቻ ሁለገብ 

የገበሬዎች ህብረት ስራ ዩኒየን የወተት ማምረቻ፣ማቀነባበሪያ እና 

የግብይት ማዕከል ስራ አስጀመሩ 

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 ፦የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል 

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር))በሀዲያ ዞን የሊቻ 

ሁለገብ የገበሬዎች ህብረት ስራ ዩኒየን የወተት ማምረቻ፣

ማቀነባበሪያ እና የግብይት ማዕከል ስራ አስጀመሩ

Read more
ሀገራዊ ለውጡ እውን የሆነበትን 8ኛ ዓመት እና ሰባተኛውን ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በማስመልከት በኢንሴኖ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሔደ ነው

ሀገራዊ ለውጡ እውን የሆነበትን 8ኛ ዓመት እና ሰባተኛውን 

ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በማስመልከት በኢንሴኖ ከተማ 

የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሔደ ነው 

ሆሳዕና፣ግንቦት 14/2018፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል
ሀገራዊ ለውጡ እውን የሆነበትን 8ኛ ዓመት እና ሰባተኛውን 

ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በማስመልከት በምስራቅ ጉራጌ ዞን 

በኢንሴኖ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ 

የድጋፍ ሰልፍ እየተካሔደ ነው 

በህዝባዊ የድጋፍ ሰልፉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል 

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )

፣የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን፣

የክልል፣የዞን የስራ ኃላፊዎች እና የብልጽግና ፓርቲ 

ደጋፊ አባላት ተገኝተዋል። 

ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሔደ 

በሚገኘው ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ ላይ ምርጫዬ ብልጽግና ነው፣

የምግብ ሉአላዊነት ተምሳሌት፣በዲጂታል ኢትዮጵያ ነገን መገንባት፣

ጸጋን ወደ ሀብት፣ብልጽግናን እመርጣለሁ አሻራዬን አኖራለሁ፣

ትላንትን ማከም ነገን መተለም እና ሌሎችም መፈክሮች

ተስተጋብተዋል።

 

Read more
የቤተሰብ እና የማህበረሰብ ብልጽግና ማረጋገጥ አብይ አጀንዳዎቻችን ናቸው :- ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

የቤተሰብ እና የማህበረሰብ ብልጽግና ማረጋገጥ አብይ አጀንዳዎቻችን ናቸው :- 

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) 

ሆሳዕና፣ግንቦት 13/2018፦ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ 

መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)በስልጤ ዞን ሳንኩራ ወረዳ 

የባለ ብዙ መንደር የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት እና ሳኒቴሽን 

ፕሮጀክት መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አደረጉ 

ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

እንደገለጹት የቤተሰብ እና የማህበረሰብ ብልጽግና ማረጋገጥ የመንግስት 

እና የብልጽግና ፓርቲ አብይ አጀንዳዎች ናቸው ብለዋል። 

ውሃ ለማህበረሰቡ የሚሰጠው ጠቀሜታ ዘርፈ ብዙ ነው ሲሉም 

ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል። 

የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ድጋፍ ላደረጉ 

አካላት ርዕሰ መስተዳድሩ ምስጋና አቅርበዋል። 

ብልጽግና ፓርቲ እና መንግስት በተለያየ ጊዜ የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶችን 

በማጠናቀቅ የህዝብ ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ ረገድ ተወዳዳሪ የሌለው 

ስራ ተግባራዊ እያደረጉ ነው ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል። 

የተመረቁ ፕሮጀክቶችን ህዝቡ በአግባቡ እንዲጠብቅ እና እንዲያስተዳድር 

ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል። 

የሳንኩራ ወረዳ ህዝብ ከመላው አመራር ጋር በመሆን በክልሉ ተግባራዊ በሚደረጉ 

የልማት ስራዎች ላይ ተጨማሪ አቅም እየፈጠሩ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ 

አስረድተዋል። 

የወረዳው ህዝብ እና አመራሩ በሰላም ፣በገቢ ፣በትምህርት፣ ጤና፣በንግድ፣ 

እና በኢንቬስትመንት ዘርፎች የላቀ ጥረት በማድረግ ላይ መሆናቸውን 

ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።

Read more
ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በስልጤ ዞን ሳንኩራ ወረዳ የባለ ብዙ መንደር የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አደረጉ::

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በስልጤ ዞን ሳንኩራ ወረዳ

የባለ ብዙ መንደር የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት መርቀው 

ለአገልግሎት ክፍት አደረጉ:: 

ሆሳዕና፣ ግንቦት 13/2018፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)በስልጤ ዞን ሳንኩራ ወረዳ የባለ ብዙ መንደር የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት እና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት 

መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አደረጉ 

የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቱ ከ 429 ሚሊየን በላይ ብር ወጪ የተደረገበት ሲሆን 

ለ 69ሺ 825 ህዝብ ተጠቃሚ ያደርጋል። 

በወረዳው ለረጅም አመታት የህዝብ ጥያቄ የነበረው የንጹህ መጠጥ ውሃ ፍላጎት

 አሁን ምላሽ አግኝቶ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።

 

Read more
የተጀመሩ የሰላም እና የልማት ስራዎችን ቀጣይነት አጠናክረን እንቀጥላለን _ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) 

የተጀመሩ የሰላም እና የልማት ስራዎችን ቀጣይነት አጠናክረን እንቀጥላለን _ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) 

ሆሳዕና፣ግንቦት 11/2018፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል
ሀገራዊ ለውጡ እውን የሆነበትን 8ኛ ዓመት እና ሰባተኛውን ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በማስመልከት በሀዲያ ዞን አመካ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ የድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል 

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )በድጋፍ ሰልፉ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት ብልጽግና ፓርቲ 

የተሞከረ፣ያደገ፣ በፈተናዎች ውስጥ ያለፈ፣ የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ራሱን የአፍሪካ እና የአለም ፓርቲ ለማድረግ እራሱን ያዘጋጀ ፓርቲ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ በአብነት ጠቅሰዋል። 

ብልጽግና የሚመራው መንግስት በ2023 እና በ2040 በአፍሪካ እና በአለም አቀፍ ደረጃ አብነት ለመሆን እየተጋ ያለ ፓርቲ ስለመሆኑም ርዕሰ መስተዳድሩ አስረድተዋል። 

ይህን የፓርቲውን አላማና ግብ በመገንዘብ ህዝቡ ላሳየው ጥልቅ ፍቅር እና ድጋፍ ርዕሰ መስተዳድሩ በራሳቸው እና በክልሉ መንግስት ስም ምስጋና አቅርበዋል። 

የአካባቢው ህዝብ ጠንካራ የስራ ባህል ያለው እና የወደፊት ብልጽግናውን እውን ለማድረግ መዘጋጀቱን ርዕሰ መስተዳድሩ አስገንዝበዋል። 

ከ15 ቀናት በኋላ ግንቦት 24 በሚካሔደው ሰባተኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ህዝቡ ብልጽግና ፓርቲን በመምረጥ ወደ መደበኛ የልማት ስራው እንዲሰማራ ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል። 

ምርጫው ሰላማዊ ፍትሀዊ፣ ተአማኒና ነጻ እንዲሆን የጋራ ትብብርና ጥረት ማድረግ ይጠበቃል ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል። 

የተጀመሩ የሰላም እና የልማት ስራችንን ቀጣይነት ማረጋገጥ አብይ ጉዳያችን ናቸው ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ በመልዕክታቸው ጠቅሰዋል። 

ብልጽግና ፓርቲን በመምረጥ ደስታችንን በጋራ ማጣጣም ይገባናል ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ መልዕክታቸውን ቋጭተዋል።

Read more
በህዝቦች መካከል ልዩነት ለመፍጠር የሚጥሩ አካላት ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) አሳሰቡ

በህዝቦች መካከል ልዩነት ለመፍጠር የሚጥሩ አካላት ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባ 

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) አሳሰቡ 

Read more
ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝቦች የጋራ ባህላዊ እሴት መገለጫ የሆነውን የእንሰት ተክል አምሳያ ቅርጽ በወልቂጤ ከተማ መርቀው ከፈቱ፡፡

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝቦች የጋራ ባህላዊ እሴት መገለጫ የሆነውን የእንሰት ተክል አምሳያ ቅርጽ በወልቂጤ ከተማ መርቀው ከፈቱ፡፡ 

 

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) 20ኛውን የኢትዮጵያ የብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን ምክንያት በማድረግ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝቦች የጋራ ባህላዊ እሴት መገለጫ የሆነውን የእንሰት ተክል አምሳያ ቅርጽ መርቀው ከፍተዋል።

Read more