Skip to main content

                                                                                    የህግ እና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ጽ/ቤት

                                                  የህግ እና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ጽ/ቤት

  •   የሪፎርም ኘሮግራሞች ጉዳዮችን አተገባበርን ይከታተላል፣ ይደግፋል ግብረ መልስ እንዲሰጥባቸው ያደርጋል፣ 
  •   የመልካም አስተዳደር ፖኬጆች አተገባበርና ዉጤታማነትን በተመለከተ የፋይዳ ዳሰሳ ጥናት ያከናውናል፣ 
  •   በየደረጃው የተዋቀሩ የፀጥታ ምክር ቤቶች ኃላፊነታቸውን በአግባቡ በሚወጡበት አግባብ የመደገፍና የመከታተል ስራ ይሰራል፣
  •   የፀጥታ ሴክተሩ የተጣለበትን ኃላፊነት በአግባቡ ሊወጣ በሚችለበት አግባብ አፈፃፀሙን የመከታተልና የመደገፍ ስራ ይሰራል፣
  •   በአጎራባች ክልሎች ድንበር አካባቢዎች የሠላምና የልማት ስራዎች በቅንጅት እንዲከናወኑ ይደግፋል፣
  •   ወቅታዊ አጠቃላይ የፀጥታ ሪፖርቶችን በመቀበል፣ በመተንተንና ዕንድምታዎችን ለይቶ ሪፖርት የማቅረብና ግብረ መልስ እንዲሰጥባቸው ያደርጋል፣
  •   አስተዳደራዊ ቅሬታዎችንና አቤቱታዎችን ይቀበላል፣ ያጣራል ውሳኔ እንዲያገኙ ያደርጋል፣ 
  •   የቅሬታናአቤቱታ መንስኤዎች ላይ ጥናት በማካሄድ ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኙ ይሰራል፣
  •   በየደረጃዉየሚገኙ የቅሬታና አቤቱታ መዋቅሮችን ይከታተላል ይደግፋል፣
  •   በየደረጃዉ የሚገኙ የቅሬታና አቤቱታ መዋቅሮች ላይ የሚሰሩ ፈፃሚዎችን አቅም የማሳደግ ስራዎችን ይሰራል፣ 
  •   የህግ ታራሚዎች ይቅርታ እንዲያገኙ ያቀረቡትን ጥያቄ ተገቢነት በማጣራት ለክቡር ርዕሰ መስተዳድሩ አቅርቦ ይቅርታ እንዲያገኙ ይሰራል፣
  •   የሰብአዊ መብቶች አያያዝና የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ እንዲሻሻል የሚያስችል አሰራር እንዲኖር ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በቅንጅት ይሰራል፣ 
  •   በተቋማትና በክልሉ ፍትህ ቢሮ ተዘጋጅተው የሚቀርቡ ረቂቅ ህጎችን የመመርመር እና ለመስተዳድር ምክር ቤቱ ማብራሪያ የማቅረብ ስራ ይሰራል፣
  •    የሌሎች ተቋማትን ረቂቅ ህጎች መሰረታዊ የህግ መርሆዎችን የተከተሉ መሆናቸዉንና አስፈላጊነታቸዉን አጣርቶ አስተያየትና የህግ ምክር ይሰጣል፣ 
  •    በህግ ጉዳዮች ላይ ለመስተዳድር ም/ቤቱም ሆነ ለርዕሰ-መስተዳድሩ ተገቢውን ሙያዊ  አስተያየትና የመፍትሄ አማራጮችን የማቅረብ ስራ ይሰራል፣
  •    የፍትህ ስርአት ማሻሻያ ፕሮግራም በሚመለከታቸው ተቋማት ተቀናጅቶ ሊተገበር በሚችልበት ሁኔታ መታቀዱንና መከናወኑን በመከታተል ለርዕሰ መስተዳድሩ ሪፖርት በማቅረብ ግብረ መልስ እንዲሰጥበት ያደርጋል፣
  •    በክልሉ ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን በመከላከል ዙሪያ በተለያዩ ተቋማት የሚከናወኑ ተግባራትን የመከታተልና የመደገፍ ስራ ይሰራል፣
  •    ምርጥ ተሞክሮዎችን መለየት፣ መቀመርና የማስፋት ስራ መስራት፡፡