Skip to main content

                                                                የርዕሰ መስተዳድርና መስተዳድር ምክር ቤት ጽ/ቤት

Mr. Semman Shifa Leggeso
  

                                          የርዕሰ መስተዳድርና መስተዳድር ምክር ቤት /ቤት ዋና ዋና ተግባርና ኃላፊነት

  •    የርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት የሰው ሀይል እና ሎጅስቲክስ እንዲሟላ ያደርጋል፣
  •   የመስተዳድር ምክር ቤቱን የስብሰባ ሂደቶች በመቅረፀ-ምስል፣ መቅረፀ-ድምፅና በህትመት ሠነዶችን በአግባቡ በመያዝና በመጠበቅ ለሚፈቀድላቸዉ አካላት የማቅረብ ስራ ይሰራል፣
  •    የመስተዳድር ምክር ቤቱን ቃለ-ጉባዔ መያዝ እና የሚተላለፉ ዉሳኔዎች ምስጢራዊነታቸዉ ተጠብቆ ለሚመለከተዉ አካል ተደራሽ እንዲሆኑ ያደርጋል፣
  •    ለካቢኔ የሚቀርቡ ጉዳዮች በመስተዳድር ምክር ቤት አሰራር ደንብ መሰረት ተገቢውን የጥራት ደረጃ ጠብቀው መቅረባቸውን ያረጋግጣል፡፡
  •    የክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት የሚያፀድቃቸዉን ደንቦችና መመሪያዎች አሳትሞ ለሚመከታቸው አካላት እንዲሰራቹ ያደርጋል፣
  •   ከመንግስት መ/ቤቶች ውሳኔ እንዲሰጥባቸው ለውይይት የሚቀርቡ ሰነዶችና የውሳኔ ሀሳቦችን በተመለከተ የማማከር፣ ድጋፍ የመስጠትና የማስተባበር ስራ ይሰራል፣
  •    በመስተዳድር ም/ቤቱ ለሚቋቋሙ ልዩ ልዩ ኮሚቴዎች ድጋፍ የመስጠትና የማስተባበር ስራ ይሰራል፣
  •    በዞኖች፣ በልዩ ወረዳዎችና ወረዳዎች የካቢኔ የአሰራር ስርዓት ደንቡን የተከተለ ስለመሆኑ ክትትልና ድጋፍ ያደርጋል፣
  •    ከዞን እና ልዩ ወረዳዎች የሚቀርቡ የኢንቨስትመንት ጥያቄዎችን ተገቢነት በማጣራት፣ ፕሮጀክቶቹ እንዲገመገሙ በማድረግ ለክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት በማቅረብ ያስወስናል፤ ውሳኔዎቹንም ለዞኖችና ለልዩ ወረዳዎች በደብዳቤ ያሳውቃል፤
  •   ከዞን እና ልዩ ወረዳዎች የሚቀርቡ የምትክ መሬት ጥያቄዎችን ተገቢነት በማጣራት፣ ጥያቄዎቹ በክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ እንዲገመገሙ በማድረግ በሚቀርበው የአስተያየትና የውሳኔ ሀሳብ መነሻ ውሳኔዎቹን ለዞኖችና ለልዩ ወረዳዎች በደብዳቤ ያሳውቃል፤
  •    በክልሉ ከሚገኙ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት፣ ከዞንና ልዩ ወረዳ መዋቅሮች እንዲሁም ከግለሰቦች የሚቀርቡ የድጋፍ፣ የትብብር፣ የምደባ እና ሌሎች ጥያቄዎችን ተቀብሎ በመመርመር ውሳኔ እንዲያገኙ ያደርጋል፣
  •    ለክልሉ ርዕሰ መስተዳድርና ምክትል ርዕሰ መስተዳድሮች፣ ከሀገር ውስጥም ሆነ ከውጪ ሀገር ወደ ክልሉ ለሚመጡ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ አምባሳደሮችና የአለምአቀፍ ድርጅቶች ተጠሪዎች የፕሮቶኮል ሽፋን የመስጠት አገልግሎት፣