Skip to main content

በክልሉ በግብርናው ዘርፍ እየተመዘገበ ያለውን የላቀ ውጤት ቀጣይነት 

ማረጋገጥ ይገባል:-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) 

ሆሳዕና፣ሐምሌ 28/2018የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር

እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ እና በቀቤና ልዩ ወረዳ 

በኩታ ገጠም እየለማ ያለ የበቆሎ ማሳ ተመልክተዋል 

ርዕሰ መስተዳድሩ በመስክ ምልከታቸው እንደገለጹት በክልሉ በግብርናው 

ዘርፍ እየተመዘገበ ያለውን የላቀ ውጤት ቀጣይነት ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል። 

በቀቤና ልዩ ወረዳ ፍቃዱ ቀበሌ ከ16ሺ ሄ/ር በላይ ማሳ በበቆሎ ክላስተር 

እየለማ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል። 

በአበሽጌ ወረዳ ደግሞ 39ሺ ሄ/ር ማሳ በበቆሎ ክላስተር መልማቱንም ርዕሰ 

መስተዳድሩ ጠቁመዋል። 

በሁለቱ አጎራባች ወረዳዎች የግብርና ልማት ስራው በተጠናከረ መልኩ እየለማ 

ነው ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል። 

በጋራ ሆኖ መስራት ውጤታማ እንደሚያደርግ ከሁለቱ አካባቢዎች ተገንዝበናል 

ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ የግብርና ግብአት አጠቃቀም እና መካናይዜሽንን ማስፋፋት 

ለምርታማነት ማደግ ወሳኝ መሆኑን አብራርተዋል። 

በቀቤና ልዩ ወረዳ ፍቃዱ ቀበሌ በቆሎ በሄክታር ከ90 እስከ 110 ኩንታል እየተመረተ 

መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ በአብነት ጠቅሰዋል። 

በተመሳሳይ በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ ደግሞ በቆሎ በሄክታር ከ90 እስከ 120 ኩንታል 

ማምረት እንደሚቻል አመላክተዋል። 

በሁለቱ አካባቢዎች የተገኘው የምርታማነት እድገት እንደ ክልልም ሆነ እንደ ሀገር ልምድ 

ይወሰድበታል ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል። 

አርሶ አደሮች ከግብርና ባለሙያዎች የሚሰጣቸውን ሙያዊ ድጋፍ በመጠቀም እና 

በትብብር መስራት በመቻላቸው በዘርፉ የላቀ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ርዕሰ 

መስተዳድሩ ተናግረዋል። 

በክልሉ ቅድመ በልግ እና ጸደይን በመጨመር አምስት የአዝመራ ወቅቶችን መጠቀም 

በመቻሉ የምርታማነት መጠን እያደገ መሆኑን በአብነት ጠቅሰዋል። 

በክልሉ የግብርናው ዘርፍ ሀብት የመፍጠር እና ወደ መካናይዜሽን የመሻገር አቅም

እየጨመረ ነው ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል። 

የአርሶ አደሮችን ኑሮ ለመቀየር የገጠር ኮሪደር ማስፋፋት አስፈላጊ ስለመሆኑም 

ርዕሰ መስተዳድሩ አመላክተዋል። 

በተያዘው የምርት ዘመን የዝናብ እጥረት ማጋጠሙን የተናገሩት ርዕሰ መስተዳድሩ 

ልዩ ልዩ ጫናዎችን በመቋቋም በግብርና ልማት ስራቸው ለውጥ ለማምጣት እየተጉ 

ላሉ አርሶ አደሮች ርዕሰ መስተዳድሩ ምስጋና አቅርበዋል።

Image