Skip to main content

ክቡር ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በዱራሜ ከተማ

ከሰንበት እስከ ሰንበት የገበያ ማዕከል መርቀው ስራ አስጀመሩ

ሆሳዕና ፣ ሰኔ 19 / 2018 የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር

 እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በከንባታ ዞን በዱራሜ ከተማ ከሰንበት እስከ

ሰንበት የገበያ ማዕከል መርቀው ስራ አስጀምረዋል

በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ግንባታው የተጠናቀቀው የዱራሜ ከተማ

ከሰንበት እስከ ሰንበት የግብይት ማዕከል 15 ሚሊየን ብር ወጪ ተደርጎበታል።

በማዕከሉ የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርት ቀርቦ ግብይት እየተካሔደበት

ሲሆን የግብይት ማዕከሉ ሳምንቱን ሙሉ አገልግሎት ይሰጣል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ሰኔ

2017 ዓ.ም የዱራሜ ከተማ ከሰንበት እስከ ሰንበት የገበያ ማዕከል የመሰረት

ድንጋይ በማስቀመጥ የግንባታ ስራ ማስጀመራቸው ይታወሳል።

በምረቃ መርሐ ግብሩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት

ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ፣የክልሉ የብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ

አቶ አቡቶ አኒቶ፣የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዘዳንት አቶ ኤርሲኖ አቡሬ

፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ፣በምክትል ርዕሰ

መስተዳድር ማዕረግ የክላስተር አስተባባሪዎች ፣ የከንባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ

አቶ አረጋ እሸቱን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

Image