Skip to main content

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ዶ/ር በዱራሜ ከተማ 

መሶብ - የአንድ ማዕከል አገልግሎት መርቀው ከፈቱ።

ሆሳዕና ሰኔ 19 ፣ 2018 ዓ.ም የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል 

መንግስት ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ( ዶ/ ር ) 

በከንባታ ዞን ዱራሜ ከተማ የተገነባውን መሶብ - የአንድ ማዕከል 

በዛሬው እለት መርቀው ከፈቱ።

"መሶብ-የአንድ ማዕከል አገልግሎት " በአንድ ጣራ ስር የተለያዩ 

የመንግስት አገልግሎቶችን በማጣመር የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን 

በመጠቀም አገልግሎት እንደሚሰጥ ተመላክቷል።

የአሰራር ስርዓቱ ዜጎች የተሟላ የዲጂታል አማራጮችን በመጠቀም 

በቀላሉ የተለያዩ የመንግስት ተቋማትን አገልግሎት እንዲያገኙ እንደሚያስችል 

ተመላክቷል።

መሶብ - የአንድ ማዕከል አገልግሎት በአንድ ስፍራ በ6 ተቋማት 

20 አገልግሎቶችን እንደሚሰጥ ተመልክቷል።

 

 

Image