Skip to main content

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) በክልሉ ባለፉት ሁለት 

ዓመታት ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የተከናወኑ ተግባራት 

አፈጻጸም ሪፖርት በጽህፈት ቤታቸው እየገመገሙ ነው 

ሆሳዕና፣ሐምሌ 18/2018፦የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር 

እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በክልሉ ባለፉት ሁለት ዓመታት ከተረጂነት ወደ 

ምርታማነት ለመሸጋገር የተከናወኑ ተግባራት አፈጻጸም ሪፖርት 

በጽ/ቤታቸው እየገመገሙ ነው 

ርዕሰ መስተዳድሩ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ብሎም 

ከተረጂነት ለመሸጋገር ባለፉት ሁለት ዓመታት በሰባት መዋቅሮች በ35 ወረዳዎች 

ልዩ ልዩ ስራዎች ተግባራዊ ሲደረግ ቆይቷል ብለዋል። 

በሁለት ዓመታት ጊዜ ውስጥ የተገኘውን ሀብት መነሻ በማድረግ በወረዳዎች 

እቅድ ተዘጋጅቶ ስራው ሲመራ መቆየቱን ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቅሰዋል። 

ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር በተከናወኑ ተግባራት ክልሉ ሰብአዊ 

ድጋፍ በራስ አቅም መሸፈን የሚያስችለውን ስርዓት መዘርጋት ስለመቻሉም 

ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል። 

ከጥቅምት 30/2019 ጀምሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከተረጂነት ለመውጣት ዝግጅት 

እየተደረገ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ በንግግራቸው አመላክተዋል። 

ይህን ተከትሎም በክልሉ የሰብአዊ ድጋፍ ሉአላዊነት ለማስጠበቅ የተሟላ ዝግጅት 

በማድረግ የጋራ ተግባቦት መፍጠር የሚያስችል መድረክ ስለመሆኑም አስረድተዋል። 

የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ማዕረጉ ማቲዎስ በክልሉ ባለፉት 

ሁለት ዓመታት ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የተከናወኑ ተግባራት አፈጻጸም 

ሪፖርት እያቀረቡ ነው።

Image