Skip to main content

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) 3ኛው የትምህርት ሴክተር ጉባኤ 

አስመልክቶ የተዘጋጀ የፈጠራ ስራዎች ኤግዚቢሽን እና የፎቶ አውደ ርዕይ 

መርቀው ለእይታ ክፍት አደረጉ 

ዘላቂ የትምህርት ጥራት ለላቀ የመማር ውጤት እና ብልጽግና በሚል መሪ 

ሀሳብ 3ኛው የትምህርት ሴክተር ጉባኤ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው። 

በኤግዚቢሽኑ ልዩ ልዩ የፈጠራ ስራዎች ቀርበው ለእይታ ክፍት የተደረጉ ሲሆን 

የክልሉ ትምህርት ቢሮ በ2018 በጀት አመት ያከናወናቸውን ስራዎች የሚያስቃኝ 

የፎቶ አውደ ርዕይ ቀርቧል።

Image