Skip to main content

በህዝቦች መካከል ልዩነት ለመፍጠር የሚጥሩ አካላት ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባ 

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) አሳሰቡ 

Image
Title

በህዝቦች መካከል ልዩነት ለመፍጠር የሚጥሩ አካላት ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባ 

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) አሳሰቡ 

ሆሳዕና፣ግንቦት 11/2018 ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል
ሀገራዊ ለውጡ እውን የሆነበትን 8ኛ ዓመት እና ሰባተኛውን ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በማስመልከት በጉራጌ ዞን በቆሴ ከተማ 

የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሔደ ነው 

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ላለፉት ጥቂት ዓመታት የህዝቡን ሰላማዊ ኑሮ ፈታኝ የሚያደርጉ ችግሮች ማጋጠማቸውን ተናግረዋል። 

የተለየ የግል ፍላጎት ያላቸው አካላት በሀዲያ እና በጉራጌ ዞን ህዝቦች መካከል ቅራኔ እንዲፈጠር 

እያደረጉት ያለውን ሴራ ህዝቡ በጋራ ማክሸፍ ይጠበቅበታል ብለዋል። 

በህዝቦች መካከል ልዩነት ለመፍጠር የሚጥሩ አካላት ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባም ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል። 

በአካባቢው የትምህርት እና የጤና ተቋማት በተፈጠረው የጸጥታ ችግር ምክንያት አገልግሎት መስጠት እንዳይችሉ 

ፈታኝ ጊዜያት ማጋጠሙን ርዕሰ መስተዳድሩ አስታውሰዋል። 

ማህበረሰቡ የመደማመጥ፣በአንድነት የመኖር እና የመተሳሰብ እሴቶቹን ይበልጥ አጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል። 

ነጠላ ትርክት ሀገርን ህዝብን ብሎም ከተሞችን ያፈርሳል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ የጋራ ትርክት ደግሞ ሀገር ይገነባል ብለዋል። 

ባለፉት ጥቂት ወራት የጸጥታ ኃይሉ የሁለቱም ዞኖች አመራሮች እንዲሁም የሀገር ሽማግሌዎች ያደረጉት ጥረት ውጤታማ ነው ብለዋል። 

የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት መደበኛ ስራ መጀመራቸውን የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ በቀሪ ጊዜያት ተማሪዎች ትምህርታቸውን

 የሚከታተሉበትን ስርዓት መፍጠር ተገቢ ነው ብለዋል። 

የጉራጌ እና የሀዲያ ህዝብ እንደ ሰርገኛ ጤፍ መለየት ያስቸግራል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ ከዚህ ቀደም የነበረውን 

አብሮነት እና መተሳሰብ ወደነበረበት መመለስ ተገቢ ስለመሆኑ ጠቅሰዋል። 

የሀገር ሽማግሌዎች እና የሀይማኖት አባቶች ሰላምን በማጽናት ረገድ ጉልህ አበርክቶ እንዳላቸው አሳስበዋል። 

የሁለቱም ዞኖች ህዝቦች በመመካከር በአካባቢው ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥ በጋራ ሊተጉ እንደሚገባም ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል። 

ግንቦት 24 በሚካሔደው ጠቅላላ ምርጫ ብልጽግና ፓርቲን እንዲመርጡ ርዕሰ መስተዳድሩ ጥሪ አቅርበዋል።