Skip to main content

የተጀመሩ የሰላም እና የልማት ስራዎችን ቀጣይነት አጠናክረን እንቀጥላለን _ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) 

ሆሳዕና፣ግንቦት 11/2018፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል
ሀገራዊ ለውጡ እውን የሆነበትን 8ኛ ዓመት እና ሰባተኛውን ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በማስመልከት በሀዲያ ዞን አመካ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ የድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል 

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )በድጋፍ ሰልፉ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት ብልጽግና ፓርቲ 

የተሞከረ፣ያደገ፣ በፈተናዎች ውስጥ ያለፈ፣ የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ራሱን የአፍሪካ እና የአለም ፓርቲ ለማድረግ እራሱን ያዘጋጀ ፓርቲ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ በአብነት ጠቅሰዋል። 

ብልጽግና የሚመራው መንግስት በ2023 እና በ2040 በአፍሪካ እና በአለም አቀፍ ደረጃ አብነት ለመሆን እየተጋ ያለ ፓርቲ ስለመሆኑም ርዕሰ መስተዳድሩ አስረድተዋል። 

ይህን የፓርቲውን አላማና ግብ በመገንዘብ ህዝቡ ላሳየው ጥልቅ ፍቅር እና ድጋፍ ርዕሰ መስተዳድሩ በራሳቸው እና በክልሉ መንግስት ስም ምስጋና አቅርበዋል። 

የአካባቢው ህዝብ ጠንካራ የስራ ባህል ያለው እና የወደፊት ብልጽግናውን እውን ለማድረግ መዘጋጀቱን ርዕሰ መስተዳድሩ አስገንዝበዋል። 

ከ15 ቀናት በኋላ ግንቦት 24 በሚካሔደው ሰባተኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ህዝቡ ብልጽግና ፓርቲን በመምረጥ ወደ መደበኛ የልማት ስራው እንዲሰማራ ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል። 

ምርጫው ሰላማዊ ፍትሀዊ፣ ተአማኒና ነጻ እንዲሆን የጋራ ትብብርና ጥረት ማድረግ ይጠበቃል ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል። 

የተጀመሩ የሰላም እና የልማት ስራችንን ቀጣይነት ማረጋገጥ አብይ ጉዳያችን ናቸው ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ በመልዕክታቸው ጠቅሰዋል። 

ብልጽግና ፓርቲን በመምረጥ ደስታችንን በጋራ ማጣጣም ይገባናል ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ መልዕክታቸውን ቋጭተዋል።

Image
Title

የተጀመሩ የሰላም እና የልማት ስራዎችን ቀጣይነት አጠናክረን እንቀጥላለን _ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)