Skip to main content

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)በሆሳዕና ከተማ 

ከሰንበት እስከ ሰንበት የገበያ ማዕከል መርቀው ስራ አስጀመሩ 

ሆሳዕና ፣ ሰኔ 9/2018) የማዕከላዊኢትዮጵያ ክልል 

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በሀድያዞን በሆሳዕና ከተማ 

ከሰንበት እስከ ሰንበት የገበያ ማዕከል መርቀው ስራ አስጀምረዋል 

በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ግንባታው የተጠናቀቀው የሆሳዕና ከተማ 

ከሰንበት እስከ ሰንበት የግብይት ማዕከል 15 ሚሊየን ብር ወጪ ተደርጎበታል። 

የግብይት ማዕከሉ ሳምንቱን ሙሉ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ሲሆን 

አምራቹን እና ሸማቹን ማህበረሰብ በቀጥታ በማገናኘት የኑሮ ውድነቱን 

በማረጋጋት ረገድ የጎላ ሚና እንዳለውም ተጠቁሟል። 

በማዕከሉ የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርት ቀርቦ ግብይት

እየተካሔደበት ነው። 

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ሰኔ 5/2017 ዓም የሆሳዕና ከተማ 

ከሰንበት እስከ ሰንበት የገበያ ማዕከል የመሰረት ድንጋይ በማስቀመጥ 

የግንባታ ስራ ማስጀመራቸው ይታወሳል። 

በምረቃ መርሐ ግብሩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 

ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ፣የክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዝዳንት 

አቶ ኤርሲኖ አቡሬ፣ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ፣

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክላስተር አስተባባሪዎች፣

የሀድያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቲዎስ አኒዮ፣ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ 

የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

Image