Skip to main content

በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ህዝቡ የሰጠንን ይሁንታ ወደ 

ላቀ ከፍታ ለማሸጋገር መትጋት ይገባል:-ርዕሰ መስተዳድር 

እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) 

ሆሳዕና ፣ሰኔ 16/2018 በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የ2018 ዓም 

የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማብሰሪያ ፕሮግራም 

በሀላባ ቁሊቶ ከተማ እየተካሔደ ነው 

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) 

እንደገለጹት በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ህዝቡ የሰጠንን ይሁንታ ወደ 

ላቀ ከፍታ ለማሸጋገር መትጋት ይገባል ብለዋል። 

በጎነት የመስጠት እና የማካፈል መርህ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ 

በተለይ ተማሪዎችን ማስተማር፣በስነ ምግባር እንዲታነጹ በማድረግ 

ለቀጣዩ አመት ዝግጁ እንዲሆኑ መደገፍ ይገባል። 

ከእውቀት ሽግግር ባለፈ ሀብትን እና ጊዜን በማካፈል የበጎ ፈቃድ 

አገልግሎት ስራ ማከናወን ይገባል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ ለዚህም 

የሁሉንም አካላት ተሳትፎ እና ትብብር ይጠይቃል ብለዋል። 

የመተሳሰብ እና የመደጋገፍ እሴትን በማጎልበት የሰዎችን ስሜት መረዳት 

የበጎነት መገለጫ ስለመሆኑም ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል። 

የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የድህነትን ቅነሳ አንዱ አካል ነው ያሉት 

ርዕሰ መስተዳድሩ መተባበርን እና አብሮነትን የምናጸናበትን እድል 

የሚፈጥር ነው ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ በንግግራቸው አመላክተዋል። 

በመረዳዳት ውስጥ የጋራ ትርክትን የምንፈጥርበት ነው ያሉት 

ርዕሰ መስተዳድሩ በተለይ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ህዝቡ የሰጠንን 

ይሁንታ ወደ ላቀ ከፍታ ለማሸጋገር መትጋት ይገባል ብለዋል።

Image